Popular Posts

Friday, October 14, 2011

ትልቁ እንጀራ*

እንጀራ ሊጋግሩ
ሰዎች ተሰበሰቡ
ኩበት ፋንድያ ለቀሙ
ግፋፉ እንጨት ሰበሰቡ::
..................................
ዱቄቱ ተፈጭቶ ተቦክቶ
ትልቅ እንጀራ ተጋገረ
ታዲያ ይኼኔ ሰው ሁሉ
"ሻሞሽ ሻሞሹን ጀመረ::
ህብረቱ ተበታተነ
ስብሳቦሹ ፈራረሰ
የሁሉም እጅ ያነኮረው
እንጀራው ተፎረፎተ
እንጀራው ተቆራረሰ::
//---//
*"ትልቁ ዳቦ ሊጥ ሆነ" የሚባለው ትዝ አላችሁ?
ጥቅምት 2 2004 ዓ.ም
የ አ.አ.ዩ መምህራን ጠቅላላ "ስብሳቦሽ" ላይ ሆኜ
(ይህችን ግጥም በመጻፍ ስብሳቦሹን የማስታጉል እንጀራውን የማነኩር አንድ እኔ ነኝ??)

አትልፊ ሆዴ!!

አይኖቼን ብትወጊያቸው
በልቤ አይኖች አይሻለሁ
ልቤን አቁስለሽ ብታደሚው
በምናቤ እቀርፅሻለሁ::
ከውስጡ ልጥፋ ብለሽ
በከንቱ አትፍጨርጨሪ
ራስሽን እንኳ ብታጠፊ
ውስጤ ነው ምትቀበሪ*::
//--///
*መቀበር በዚህ አግባብ መሞትን ወይም መቛጨትን እንዲያሳይ አልፈልግም:: ይልቅስ ማረፍ (መጠለል) እና ደግሞ መሰንቀር ወይም መቀርቀር(ለምሳሌ የወሊድ መቆጣጠሪያ ወይም የ...........መድሃኒት እንደሚቀበር) በሚሉት ትርጓሜዎች ይታሰብልኝ::
ሆዴ የተባልሽ ሁላ.......ግን እውነት ይመስልሻል?
ጥቅምት 2 2004 ዓ.ም
ከሰዓት
FBE አድራሽ
ስብሰባ ላይ ሆኜ(ስብሰባውን አቋርጨ በሀሳብ መንጎዴ የተገባ ነው?)

Saturday, August 6, 2011

እግዜር ይስጥልኝ ሰይጣን!!


ሰይጣን እወደሃለሁ ብዬ ባልደልልህም
ላስተማርከኝ ነገር ሁሉ ሳላመሰግን አላልፍም::
አንተ ባትፈታተነኝ በድካሜ ባልኮንታኮት በውድቀቴ ባልሰበር
አንዳንተው ትዕቢቴ ጥሎኝ ከክፉው ሲኦል ተጥዬ እነድ እሰቃይ ነበር::
ሐሙስ ሐምሌ 29 2003 ዓ.ም

የተሸወድኩት

ሸወድሽኝ ተጫወትሽብኝ
ቀለድሽብኝ አጃጃልሽኝ አቂቂያልሽኝ
እንዲህ እንዲያ ዚኒ ቁልቋል
ገለ መለ አልልሽም
ምክንያቱም አንቺ አይደለሽም::
እኔ ነኝ የተሸወድኩት
ለ እግዚአብሄር መሰውያው ላይ
ራሴን ላንቺ ያረድኩት
ላምላኬ በማጠኛው
ራሴን ላንቺ ያጠንኩት::
እኔ ነኝ የተሸወድኩት
በዚች የ እግዚአብሄር ልቤ ውስጥ
"አንቺ"ን ከ "እርሱ" ያዳበልኩት::
እኔ ነኝ የተሸወድኩት
በ እግዚአብሄር ቅዱስ ስፍራ ላይ
የክብር ጫማዬን አውልቄ
ላንቺ ክብር የሰገድኩት::
እኔ ነኝ የተሸወድኩት
ለሞተልኝ አምላኬ ሳይሆን
ለሞትኩልሽ ላንቺ የሞትኩት::

እንዲህ እንዲያ ዚኒ ቁልቋል አልልሽም
ምክንያቱም አንቺ አይደለሽም::
እኔ ነኝ የተሸወድኩት
ትልቁን "ፈጣሪዬን" ትቼ
ትንሿን "ፍጡር" ያመለኩት::

//--///
ሐምሌ 27 2003
ሳር ቤት እቤት
ሴቶችን "ለሚያመልኩ" "ላመለኩም" ሁሉ::

Wednesday, July 27, 2011

ማን እንደኔ

ማን እንደኔ ይሆናል?
ማንስ እኔን ይመስላል?
ከ አላዛር እበልጣለሁ
ከ ኢየሱስም እልቃለሁ
በየጊዜው እየሞትኩኝ
በየጊዜው እነሳለሁ::
//-//
(To "the old self, the old man" which dies and rises now and then!

To us who fall and rise every time)__sorry for the GURAMAYLE!
ሐምሌ 18 2003 ዓ.ም
4:45 ከ ምሽቱ
አፍንጮ በር
ሃሳቡ ቀደም ብሎ ቀን ላይ ተፀንሶ ነበር

Monday, July 25, 2011

ኦ ማንዴላ

ኦ ማንዴላ
የማትሰክር በጠላ
በአረቄ የማትጠነብዝ
በወይን የማትደነዝዝ::
ያን ሁሉ ስቃይ ተግተህ
ያን ሁሉ ግፍ ጠጥተህ
ሰክረህ ያልተንገዳገድከው
ይኸ ድንቅ አምላካችን
ምን ማርከሻ ቢሰጥህ ነው??

ኦ ማንዴላ
የማትሰክር በጠላ
በአረቄ የማትጠነብዝ
በወይን የማትደነዝዝ
ያን ሁሉ ዝና ጨልጠህ
ያን ሁሉ ክብር አንዶቅዱቀህ
በስልጣን አረቄዋ
በናላ አዟሪዋ እጅ ወድቀህ
ሰካራም ሆነህ ያልቀረኸው
ይኸ ግሩም ጌታችን
ምን ማርከሻ ቢሰጥህ ነው??
//-///
ሐምሌ 17 2003 &ወደ ምሽት( ነገ የ ማንዴላ 93ኛ ዓመት የልደት በዓል ይከበራል)
ፒያሳ& ኪያብ ካፌ
ከወዳጄ በረከት ጋር ስለ ማንዴላ አውርተን ውስጤ ቢነሳሳ ጊዜ ጻፍኩት
ለማንዴሎች ሁሉ ጌታ ለጌታ ኢየሱስ!!

Saturday, July 23, 2011

ነገረ-ቆብ

እውቀትን መረመርናት

ውስጠ ሚስጥሯን በልትናት

እንኳን ደስ ያለን ያሉ

የራስ ቆብ ይደፋሉ::

ደግሞ

አለምን ብንመርምር

ደስታን ከሀዘን ብንደምር

"ችቦ አይሞላም ወገቧ"

ከንቱነት ነው ቀለቧ

ትቅርብን እንፍታት ያሉ

የራስ ቆብ ይደፋሉ::

//---///

ሓምሌ 16 2003 ዓ.ም

7:58 ከሰዓት

እንቁላል ፋብሪካ

ለወዳጄ ለ ኢየሩሳሌም አሰግድ ምርቃት ግብጃ ሄጄ የጫርኩት

Saturday, July 16, 2011

ዱቤ 1

እግዚአብሄር ዱቤ ይወዳል
ፀሎት በዱቤ ይወስዳል
ግን አይደለም እንደ ሰው
በጊዜው በሰአቱ
ጨምሮ ነው ሚመልሰው::

ሓምሌ 5 2003 ከሰዓት
አፍንጮ በር አዲስ አበባ
በስራ ተወጥሬ መጣብኝ

Saturday, July 9, 2011

ሀገሬ በሰማይ?

"ሀገሬ በሰማይ ነው" ብዬ ፎክሬ ዝቼ
"ሀገሬን ከነጣጣዋ" "ለምድራውያኑ" ትቼ
ወደ ሰማያ ተነጥቄ ደጆቿን ብነካካ
"ወደ ምድር ሂድ" ተባልኩ
የአንድዬ አላማ
"ግዛት ማስፋት" ነው ለካ!

ሀምሌ 1 2003 ዓ.ም
6 ኪሎ ድህረ ምረቃ በተ-መጻህፍት

Tuesday, July 5, 2011

ፀሎተ ዘወትር


ፀሎተ ዘወትር

ስንት መንግስት ሰማን ስንት መንግስት አዬን
ስንት መንግስት አጠገበን ስንት መንግስት አሰቃዬን::
እባክህ
"መንግስተ-ምድር" ይወረድ "መንግስተ ምድር ይውጣ"
ፍቃድህ በምድር ትሁን መንግስትህ በምድር ትምጣ::

20-10-2003 .
. ቤላ ::ከጣልያን ኤምበሲ አጥር ስር
                                                                                        ጠዋት 2:30

Thursday, June 30, 2011

Energizer(ኢያሄይል)

ሃይል ጉልበትህን ልታድስ እንደ ንስር ልትፈጥን እንደ አህያ ልትበረታ
Energized ልትሆን Energizer ልትጠጣ
በዚህ የናረ ዋጋ ገንዘብህን አትከስክስ ጥሪትህን በከንቱ አታውጣ
ይልቅ ምንም ሳትከፍል የተዋረደ ልብ ይዘህ በሮችህን ብትበረግድ
የውሃ ጎተራህን ይዘህ ጸባኦት ብትወጣ ብትገሰግስ ይሻልሃል
እሱ
"ለዘላለም የሚፈልቅ" ነቭስን ሚያረሰርስ "የህይወት ውሃ ምንጭ" ያጠጣሃል
በሃይል በጉልበት ከሚሞላ ከቅዱስ መንፈሱ ያጠግብሃል!

መለያዬት ሞት ነው?

መለያዬት ሞት ነው?
"መለያዬት ሞት ነው ለተዋደደ ሰው"
ግዴለም
ከስጋ ልለያይና ደርሶብኝ ልየው ልቅመሰው::
"ነፍሱን የሚያገኝ ያጠፋታል" ስለ እሱ ሚያጠፋት ያገኛታል
ታዲያ ከሚወዱት "ስጋ" ከሚወዱት "ነቭስ" መለየትን
ህይወት እንጅ ሞት ይሉታል?!

ተዋንያን

ተዋንያን
የምትሰብከውን ኑረው እንዲሉ
የማትኖረውን አትስበክ ቢሉ
ስንት አፎች ቤተ-ስኪያኖች
ስንት መስጊዶች ይዘጋሉ!!

Wednesday, June 1, 2011

Like Forever?


Our lips come together,
And we melt in something like forever.
I descend to the sky (I think so)
She too flies high
Together, we bade the earth good-bye
And to another globe
Lost in love
She and I
We don’t really know to where
But our hearts bear no fear
We simply dissolve to somewhere
And it seems like it is forever………
Such and such they tell us
This and that way they fool us
Come on there!
There is no forever in there!!!!


Friday, May 27, 2011

God Is So Simple


God is in you
God is in me
God is in what you feel
And God is in what you see

Don’t fret
Don’t calculate
Don’t get into much trouble
Because God is so clear
And God is so simple!

                               March 1, 2011
                             While at a workshop (AAU Social science and Humanities academic staff)
·         To those of us who take ourselves to be intellectuals and miss god always expecting Him to be complex. We have failed to understand that the way the Spirit works is much simpler but still nobler than the intellect works.

Friday, May 20, 2011

Faith Has No Eyes


Faith has no eyes
For it does not need to see
Faith has no ears
For it does not need to hear

Bur even without the two
What it can see and hear
Is so open and clear
                       February 27, 2011
                        02:25 am
                        Ancho Ber, Addis Ababa

Faith Has No Eyes


Faith has no eyes
For it does not need to see
Faith has no ears
For it does not need to hear

Bur even without the two
What it can see and hear
Is so open and clear
                       February 27, 2011
                        02:25 am
                        Ancho Ber, Addis Ababa

Faith Has No Eyes


Faith has no eyes
For it does not need to see
Faith has no ears
For it does not need to hear

Bur even without the two
What it can see and hear
Is so open and clear
                       February 27, 2011
                        02:25 am
                        Ancho Ber, Addis Ababa