ሸወድሽኝ ተጫወትሽብኝ
ቀለድሽብኝ አጃጃልሽኝ አቂቂያልሽኝ
እንዲህ እንዲያ ዚኒ ቁልቋል
ገለ መለ አልልሽም
ምክንያቱም አንቺ አይደለሽም::
እኔ ነኝ የተሸወድኩት
ለ እግዚአብሄር መሰውያው ላይ
ራሴን ላንቺ ያረድኩት
ላምላኬ በማጠኛው
ራሴን ላንቺ ያጠንኩት::
እኔ ነኝ የተሸወድኩት
በዚች የ እግዚአብሄር ልቤ ውስጥ
"አንቺ"ን ከ "እርሱ" ያዳበልኩት::
እኔ ነኝ የተሸወድኩት
በ እግዚአብሄር ቅዱስ ስፍራ ላይ
የክብር ጫማዬን አውልቄ
ላንቺ ክብር የሰገድኩት::
እኔ ነኝ የተሸወድኩት
ለሞተልኝ አምላኬ ሳይሆን
ለሞትኩልሽ ላንቺ የሞትኩት::
እንዲህ እንዲያ ዚኒ ቁልቋል አልልሽም
ምክንያቱም አንቺ አይደለሽም::
እኔ ነኝ የተሸወድኩት
ትልቁን "ፈጣሪዬን" ትቼ
ትንሿን "ፍጡር" ያመለኩት::
//--///
ሐምሌ 27 2003
ሳር ቤት እቤት
ሴቶችን "ለሚያመልኩ" "ላመለኩም" ሁሉ::
No comments:
Post a Comment