Popular Posts

Friday, October 14, 2011

ትልቁ እንጀራ*

እንጀራ ሊጋግሩ
ሰዎች ተሰበሰቡ
ኩበት ፋንድያ ለቀሙ
ግፋፉ እንጨት ሰበሰቡ::
..................................
ዱቄቱ ተፈጭቶ ተቦክቶ
ትልቅ እንጀራ ተጋገረ
ታዲያ ይኼኔ ሰው ሁሉ
"ሻሞሽ ሻሞሹን ጀመረ::
ህብረቱ ተበታተነ
ስብሳቦሹ ፈራረሰ
የሁሉም እጅ ያነኮረው
እንጀራው ተፎረፎተ
እንጀራው ተቆራረሰ::
//---//
*"ትልቁ ዳቦ ሊጥ ሆነ" የሚባለው ትዝ አላችሁ?
ጥቅምት 2 2004 ዓ.ም
የ አ.አ.ዩ መምህራን ጠቅላላ "ስብሳቦሽ" ላይ ሆኜ
(ይህችን ግጥም በመጻፍ ስብሳቦሹን የማስታጉል እንጀራውን የማነኩር አንድ እኔ ነኝ??)

አትልፊ ሆዴ!!

አይኖቼን ብትወጊያቸው
በልቤ አይኖች አይሻለሁ
ልቤን አቁስለሽ ብታደሚው
በምናቤ እቀርፅሻለሁ::
ከውስጡ ልጥፋ ብለሽ
በከንቱ አትፍጨርጨሪ
ራስሽን እንኳ ብታጠፊ
ውስጤ ነው ምትቀበሪ*::
//--///
*መቀበር በዚህ አግባብ መሞትን ወይም መቛጨትን እንዲያሳይ አልፈልግም:: ይልቅስ ማረፍ (መጠለል) እና ደግሞ መሰንቀር ወይም መቀርቀር(ለምሳሌ የወሊድ መቆጣጠሪያ ወይም የ...........መድሃኒት እንደሚቀበር) በሚሉት ትርጓሜዎች ይታሰብልኝ::
ሆዴ የተባልሽ ሁላ.......ግን እውነት ይመስልሻል?
ጥቅምት 2 2004 ዓ.ም
ከሰዓት
FBE አድራሽ
ስብሰባ ላይ ሆኜ(ስብሰባውን አቋርጨ በሀሳብ መንጎዴ የተገባ ነው?)