Popular Posts

Friday, October 14, 2011

አትልፊ ሆዴ!!

አይኖቼን ብትወጊያቸው
በልቤ አይኖች አይሻለሁ
ልቤን አቁስለሽ ብታደሚው
በምናቤ እቀርፅሻለሁ::
ከውስጡ ልጥፋ ብለሽ
በከንቱ አትፍጨርጨሪ
ራስሽን እንኳ ብታጠፊ
ውስጤ ነው ምትቀበሪ*::
//--///
*መቀበር በዚህ አግባብ መሞትን ወይም መቛጨትን እንዲያሳይ አልፈልግም:: ይልቅስ ማረፍ (መጠለል) እና ደግሞ መሰንቀር ወይም መቀርቀር(ለምሳሌ የወሊድ መቆጣጠሪያ ወይም የ...........መድሃኒት እንደሚቀበር) በሚሉት ትርጓሜዎች ይታሰብልኝ::
ሆዴ የተባልሽ ሁላ.......ግን እውነት ይመስልሻል?
ጥቅምት 2 2004 ዓ.ም
ከሰዓት
FBE አድራሽ
ስብሰባ ላይ ሆኜ(ስብሰባውን አቋርጨ በሀሳብ መንጎዴ የተገባ ነው?)

No comments:

Post a Comment